በ2009 ዓ.ም መኸር ወቅት ከአነስተኛ የግል ገበሬዎች የተገኘው የምርት መጠን ከአምናዉ የመኸር ወቅት ጋር ሲነጻጸር የምርት መጠኑ የ8.83 በመቶ ወይም የ23.6 ሚሊዮን ኩንታል ጭማሪ አሳይቷል
የማዕከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ መላ ሀገሪቱን በመሸፈን ከመስከረም ወር በ2009 ዓ.ም መጀመሪያ እስከ የካቲት ወር መጨረሻ ለአምሰት ወራት ሲያካሄድ የቆየዉን የ2009 ዓ.ም የአነስተኛ ገበሬዎች የ2009 ዓ.ም. የዋናው መኸር ወቅት ድህረ-ሰብል ምርት ናሙና ጥናት ዉጤትን አስመልክቶ ሚያዚያ 19 ቀን 2009 ዓ.ም በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ በ2009 ዓ.ም የመኸር ወቅት ከ290 ሚለዮን ኩንታል በላይ ምርት መገኘቱ ተገለጸ፡፡
የኤጀንሲው የስታቲስቲክስ ጥናቶችና ቆጠራ ዘርፍ ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ አማረ ለገሰ በወቅቱ እንደገለጹት በ2009 ዓ.ም በዋናው መኽር ወቅት የሰፋፊና መካከለኛ የንግድ እርሻዎችን፣ የበጋ ወቅት የግል ገበሬዎች የመስኖ እርሻ ድህረ-ሰብል ምርትንና የበልግ ወቅት ሰብል ምርትን ሳያካትት በአነስተኛ የግል ገበሬዎች ብቻ ታርሶ በምግብ ሰብሎች የተሸፈነ መሬት ስፋት 12,574,107.33 ሄክታር ሲሆን በሰብል ዘመኑ የተገኘዉ የምርት መጠን ደግሞ 290,385,593.21 ኩንታል ነው፡፡
ኤጀንሲዉ በሰጠው መግለጫ ከምግብ ሰብሎች ከፍተኛ ጭማሪ (9.75 በመቶ) የታየው በብርዕና አገዳ ሰብሎች ምርት ላይ ነው፡፡ ጤፍ፣ ስንዴ፤ በቆሎ፣ ዳጉሳ፣ ሩዝና ሌሎችም በብርዕና አገዳ ምድብ ስር ያሉ ሰብሎች በሙሉ ጭማሪ አሳይተዋል፡፡ Read More ...