እንዳለፉት ዓመታት ሁሉ ዘንድሮም የዋናው መኸር ድህረ-ሰብል ምርት ወቅት በጌዚያዊ ና ቋሚ ሰብሎች ማለትም በአገዳ፣ ብርዕ፤ የጥራጥሬ ፣ የቅባት እህሎች ፣ በአተክልት ፣ ስራስር እና በቋሚ ሰብሎች እንሰትን ጨምሮ ተሸፍኖ የነበረውን የመሬት ስፋት እና የተመረተው የምርት መጠን ግምት በሰብል ዓይነት መገመት የሚያስችሉ መረጃዎችን ወካይ ከሆኑ ናበ ሳይንሳዊ መንገድ ከመላሀገሪቱ በተመረጡ 2,223 ናሙና የቆጠራ ቦታዎች ውስጥ ኗሪ ከሆኑ ና በናሙ ና ተመርጠው ጥናቱ በተካሄደባቸው 44,362 ቤተሰቦች ውስጥ ከሚገኙ በዘንድሮው የመህር ወቅት ሰብል በማምረት ሥራ ተሰማርተው ከነበሩ ባለይዞታ ገበሬዎች የተሰበሰበ ነው፡፡
ከላይ ቁጥራቸው በተገለጸው ለጥናቱ ተመርጠው በነበሩ የግብርና ቤተሰቦች አባል ከሆኑ ከእያንዳንዱ በዘንድሮው የመኸር ወቅት በሰብል ማምረት ሥራ ከተሰማራ ባለይዞታ ገበሬ በዘንድሮው መህር ሰብል ለማምረት ሥራ ያዋላቸው
1.በሰብል የተሸፈኑ ማሣዎች የመሬት ስፋት መጠን መረጃዎችን፣ እያንዳንዱን በየሰብል ዓይነቱ የተሸፈነ ማሳን በኦሮሚያ ክልል ጂፒኤስ፣ በተቀሩት ክልሎች ደግሞ ሜትርና ኮምፓስ በመጠቀም ተግባራዊ የማሣ ልኬት በማካሄድ ከመስክ በመሰብሰ
2.ጥቅም ላይ የዋለ የግብር ና ምርት ማሳደጊያ ግብዓቶች (ከተፈጥሮ የተገኙ እንደ ፍግ፣ የቅጠላ ቅጠልና ስራ ስር ብስባሽ እና የኬሚካል ውጤት የሆኑ ዩሪያ፣ ዳፕና የመሳሰሉ ማዳበሪያዎች፣ ፀረ-ሰብል ተባይና አረም ማጥፊያ መድሐኒቱች እና ምርጥ ዘር) መጠን መረጃዎችን በተግባር በመመዘንና ለእያንዳንዱ ባለይዞታ በሚደረግ የግል ቃለ መጠይቅ በእያንዳንዱ በሰብል የተሸፈነ ማሣ ላይ ጥቅም ላይ የዋሉ የግብርና ምርት ማሳደጊያ ግብዓቶች መጠን መረጃዎች በግብዓትና በሰብል ዓይነት ከመስክ በመሰብሰ
3.በዘንድሮው መኸር ወቅት በተካሄደው ሰብል የማምረት ሥራ የተገኘውን ጠቅላላ ምርትና የምርታማነት መጠን በሰብል ዓይነት ማስላትና በየሰብል ዓይነቱ የተገኘ ጠቅላላ የምርት መጠንን በዞን፤ በክልልና በሀገር አቀፍ ደረጃ ማቀናበር የሚያስችሉ የምርታማነት መረጃዎችን በሰብል ዓይነት ለጥናቱ ከተመረጡ ከእያንዳንዱቆጠራቦታ በዘንድሮው የመህር ወቅት በአገዳና ብርዕ፤ በጥራጥሬ በቅባት እህሎች ከተሸፈኑ ማሳዎች ለእያንዳንዱ የሰብልዓይነት 10 በሰብል ዓይነቱ የተሸፈኑ ማሣዎቸን በራንዳም/እጣ የተመረጡ ማሳዎችን በመለየት ከእያንዳንዱ የተመረጠ ማሣ የተገኝውን መረጃ በመመዝገብ፤ ከላይ የተገለጸውን አሰራር ለእያንዳንዱ የሰብል ዓይነት በተመረጡ አስር ማሣዎች በመተግበር የሚገኙ የሰብል ምርታማነት መረጃዎችን ከመስክ በመሰብሰብ ፡
በዋነኛነት ከላይ የተገለጹትንና በርካታ ተዛማጅና ሌሎች መረጃዎችን ከመስክ የመሰብሰብ ሥራ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ የመረጃዎችን ጥራትና አስተማማኝነት የማረጋገጥ ሥራ በኤጀንሲው 24 ቅ/ጽ/ቤቶች በሚገኙ የመስክ ሥራ ተቆጣጣሪዎችና ከዋናው መ/ቤት በተውጣጡ ከፍተኛ ባለሙያዎች የመስክ ቁጥጥርና ግምገማ የተካሔደ መሆኑ በጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት ተገልጿል፡፡